ggnltitl.jpg 
(8122 bytes)

Amh_mkbl.jpg (142585 bytes)

 

divider1.gif (1097 bytes)

If you cannot read the Amharic font below, you need an Amharic Unicode Font in order to read this booklet.   

Anyone can use this booklet for personal study,  one-to-one descipleship, or group descipleship.  It can be printed and distributed as long as it is distributed freely.

divider1.gif (1097 bytes)

ማውጫ

   I      ክርስቶስን መቀበል

1. ክርስቶስን መቀበል ምን ማለት ነው@

2. ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበል በሕይወታችን ምን ለውጥ ሆነ@

3.  አንድ ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንደሚገባ እርግጠኛ መሆን ይችላል@

 

     II.      በክርስቶስ ማደግ

 

1. ጸሎት

2. የእግዚብሔር ቃል

3. ከአማኞች ጋር ሕብረት ማድረግ

 

     III      ለክርስቶስ መኖር

1. ለክርስቶስ የምንኖረው እንዴት ነው@

2. ምስክርነት ምን ማለት ነው@

 

ክርስቶስን መቀበል

1. ክርስቶስን መቀበል ምን ማለት ነው@

‹‹(ኢየሱስ ክርስቶስን) ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት የእግዚአብሔር ልጆ ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡›› ዮሐ. 1$12

      ከዚህ ጥቅስ እንደምንመለከተው ኢየሱስ ክርስቶስን መቀበል የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር ቃል ውስጥ የወጣ እንጂ ሰዎች የፈጠሩት አነጋገር አይደለም፡፡ ክርስቶስን መቀበል ሲባል በተለይ እኛ ኢትዮጵያውያን ግራ እንጋባለን፣ በህፃንነታችን ክርስትና የተነሣን ስለሆንን፤ እኔ ከህፃንነቴ ጀምሮ ክርስቲያን ነኝ፤ ክርስቶስን ተቀበል የምትሉኝ እንዴት ነው የሚል ጥያቄ በአእምሮአችን ይመጣል፡፡

ከሕፃንነቴ ጀምሮ ክርስቲያን ነኝ@

      ክርስትናም ሆነ ማንኛውም ዓይነት እምነት አንድ ሰው ካደገ በኋላ አመዛዝኖ የሚቀበለው እንጂ እንደ ቤትና ርስት በውርስ የምናገኘው ነገር አይደለም፡፡ አባትየው ዶክተር ስለሆነ ልጁም ዶክተር ሆኖ እንደማይወለድ ሁሉ፤ እናትና አባቶቻችን ክርስቲያኖች ስለሆኑ እኛም ክርስትናን ወርሰን መወለድ አንችልም፡፡ የእነርሱ እምነት ለእኛ መልካም አርአያ ሆኖልናል፤ በፊሪሃ እግዚአብሔር እንድናድግ ሊረዳን ይችላል፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው የእግዚአብሔር ቃል በሚለው መሠረት ክርስቲያን መሆን የሚችለው፤

1.     ኃጢአተኛ መሆኑን ሲገነዘብ፤

‹‹ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋል የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሏቸዋል›› ሮሜ 3$23

2.     ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኃጢአቱ ሲል እንደሞተ ሲያምን፤

‹‹ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፡፡›› ሮሜ 5$8

3.     እስከ ዛሬ የሠራሁትን ኃጢአት ሁሉ ይቅር በለኝ ብሎ ከልብ ንሥሐ ሲገባና ኢየሱስ ክርስቶስን የሕይወቱ ጌታና አዳኝ አድርጎ ሲቀበል፡፡

 ‹‹እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንሥሐ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል፡፡›› ሐዋ. 17$30

        ‹‹የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻል፡፡›› 1ዮሐ. 1$7

        ‹‹እነሆ በልባችሁ ደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ በሩንም ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ እገባለሁ፡፡›› ራእ. 3$20

‹‹ይህንን ተገንዘበው ከዚህ በፊት ክርስቶስን ለመቀበል ውሳኔ አላደረጉ እንደሆን ይህንን አጭር ጸሎት ከልብ ይጸልዩ››፡፡

‹‹ጌታ ሆይ፤ ኃጢያተኛ እንደሆንኩኝ አውቃለሁ፡፡ የክርስትናን እምነት በውርስ ማግኘት እንደማይቻልም ተረድቻለሁ፡፡ ከተወለድኩ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የሠራሁትን ኃጢአት ሁሉ ይቅር በለኝ፡፡ ለእኔ ስትል ባፈሰስከው ደም እጠበኝ፡፡ ወደ ልቤ እንድትገባ የልቤን በር እከፍትልሃሁ፡፡ ና! ወደ ልቤ ግባ፤ የሕይወቴም አዳኝና ጌታ ሁን፡፡ ስለሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ አሜን››

መቀበል ስንል ምንን ያመለክታል@

መቀበል የሚለው ቃል አንድ የተሰጠ ነገር መኖሩን ያመለክታል፡፡ ሰጭ ከሌለ ተቀባይም ሊኖር አይችልም፡፡ ክርስቶስን መቀበል ስንልም ኢየሱስ ክርስቶስ ከእግዚአብሔር አብ ለዓለም ሁሉ የተሰጠ ስጦታ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በእርሱ (በኢየሱስ ክርስቶስ) የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን (ኢየሱስ ክርስቶስን) እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን (ሰዎችን) እንዲሁ ወዷልና፡፡ ዮሐ 3$16

   ከዚህ ጥቅስ እንደምንመለከተው ኢየሱስ ክርስቶስ እንድንበት ዘንድ ለዓለም ሁሉ የተሰጠ የነጻ ስጦታ ነው፡፡

   የእግዚአብሔር ቃል ኢየሱስ ክርስቶስን ተቀበሉ በሚልበት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ለኃጢአታችሁ መሥዋዕት ይሆን ዘንድ የተሠጣችሁ የዓለም መድኃኒት (መድኃኒዓለምን) ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ልባችሁ ተቀበሉት ማለቱ ነው፡፡

   አንድን መድኃኒት በእጃችን ይዘን ይህ መድኃኒት እንደሚፈውሰኝ አምናለሁ ብንል፤ በመጠጣት፤ በመዋጥ፤ ወይም በመርፌ ያንን መድኃኒት ከደማችን ጋር ካላዋሃድነው ሊፈውሰን አይችልም፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስንም ወደ ልባችን ተቀብለን የሕይወታችን ጌታ ካላደረግነው ስለ ኢየሱስ ማወቃችን ወይም መስማታችን ብቻ ከዘላለም ጥፋት አያድነንም፡፡

 

2. ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበል በሕይወታችን ምን ለውጥ ሆነ@

1. የእግዚአብሔር ልጆች ሆንን፤

ለተቀበሉት ሁሉ በስሙ ለሚያምኑት የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡ ዮሐ. 1$12

በዚህ ጥቅስ መሠረት ሰዎች ሁሉ በጅምላ የእግዚአብሔር ልጆች እንዳልሆኑ እንረዳለን፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች ለመሆን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ሕይወታችን በንሥሐና በእውነተኛ ልብ መቀበል አለብን፡፡

2. በመንፈስ ዳግም ተወለድን፤

   እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም፡፡ ዮሐ. 3$5

 እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን፡፡  ቲቶ 3$5

3. በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ሆንን፤

ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኖአል፡፡ 2ቆሮ. 5$17 

   4. ከጨለማ ወደ ብርሃን ወጣን፤

እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን (የክርስቶስን) በጎነት እንድትነግሩ የተመረጠ ትውልድ የንጉሥ ካህናት፤ ቅዱስ ሕዝብ፤ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፡፡ 1ጴጥ. 2$9

   5.  የእግዚአብሔር ወገን ሆንን፤

እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል፡፡ 1ጴጥ. 2$10

6.        ከመንፈሳዊ ሞት ወደ ዘላለማዊ ሕይወት ተሸጋገርን፤

    በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን (በመንፈስ) ነበራችሁ... ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለጠጋ ስለሆነ፤ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፡፡ ኤፌ. 2$1፤ 4-5፡፡

    እውነት እውነት እላችኋላሁ፤ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፡፡

 

3. አንድ ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንደሚገባ እርግጠኛ መሆን ይችላል@

የእግዚአብሔር ቃል በ1ዮሐ. 5$13 ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም (በኢየሱስ ክርስቶስ) ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ፡፡›› በማለት የዘላለም ሕይወት እንዳለን ማወቅ እንደምንችልና ማወቅ እንዳለብንም ያሳስበናል፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ድብብቆሽ አይጫወትም፤ ማወቅ የሚገባንን ሁሉ በቃሉ ገልጾልናል፡፡

‹‹ልጁ (ኢየሱስ ክርስቶስ) ያለው ሕይወት (የዘላለም ሕይወት) አለው ልጁ የሌለው ሕይወት የለውም፡፡›› 1ዮሐ. 5$12

በዚህ ቃል መሠረት ሰዎች ሁሉ በሁለት ይከፈላሉ፤ የዘላለም ሕይወት ያላቸውና የዘላለም ሕይወት የሌላቸው፡፡ ይህንንም የሚወስነው ኢየሱስ ክርስቶስ በሕይወታችን መኖሩና አለመኖሩ ነው፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በሕይወታችን ውስጥ ካለ የእግዚአብሔር መንፈስ፤ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ወይም የዘላለም ሕይወት እንዳለን ለመንፈሳችን እንደሚመሰክርልን የእግዚአብሔር ቃል ያስረዳል፡፡

‹‹የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ (መንፈስ ቅዱስ) እርሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል፡፡ ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለትም የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፡፡›› ሮሜ 8$16

 

በክርስቶስ ማደግ

 

‹‹እንግዲህ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደተቀበላችሁ በእርሱ ተመላለሱ፤ ሥር ሰዳችሁም በእርሱ ታነጹ፤ እንደ ተማራችሁም በሃይማኖት ጽኑ፤ ምሥጋና ይብዛላችሁ፡፡››

ክርስቶስን መቀበል ወይም መዳን የክርስትና ሕይወት ጅማሬ ነው እንጂ ፍጻሜው አይደለም፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን ከተቀበልን በኋላ በእርሱ ማደግ አለብን፡፡ በእርሱ ሥር መስደድ አለብን፡፡

በክርስትና ሕይወታችን ከህፃንነት ወደ ልጅነት፤ ከልጅነት ወደ ጎልማሳነት፤ ከጎልማሳነት ሙሉ ሰው ወደ መሆን እያደን መሄድ አለብን፡፡

‹‹ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፤ እንደ ልጅም አስብ ነበር፤ እንደ ልጅም እቆጥር ነበር፤ ጎልማሳ ሆኜ ግን የልጅነትን ፀባይ ሽሬአለሁ፡፡›› 1ቆሮ. 13$11፡፡

እድገት ጊዜ የሚወስድ ሂደት (Process) ነው፡፡ ቶሎ የሚያድግ ነገር፤ ቢኖር አረምና ሣር ብቻ ነው፡፡ ፍሬ ያለው፤ ለሰዎችም የሚጠቅም ዛፍና ተክል ሁሉ ለማደግ ጊዜ ይወስዳል፡፡  ለማደግ የሚያስፈልጉትን ነገሮችም፤ ማለትም አየር፤ ምግብ (ውሃና አንዳንድ ንጥረ ነገሮች)፤ የፀሐይንም ብርሃን በየጊዜው ማግኘት አለብን፡፡

አንድ በመንፈስ ዳግም የተወለደ ሰውም ጤናማ ሆኖ ለማደግ የሚያስፈልጉት የተለያዩ ነገሮች አሉ፡፡ እነዚህን ነገሮች በየጊዜው ካላገኘ ዕድሜ ልኩን መንፈሳዊ ህፃን ይሆናል፡፡ ወይም እድገቱ ጤናማ አይሆንም፡፡

 

ለአንድ ክርስቲያን ዕድገት የሚያስፈልጉት ነገሮች ምንድን ናቸው@

ለአንድ ተክል ዕድገት ከላይ የተጠቀሱት ሦስት የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ነገሮች እንዳሉ ሁሉ፤ ለአንድ ክርስቲያንም ዕድገት የሚያስፈልጉ ሦስት መሠረታዊ ነገሮች አሉ፡፡

እነዚህም፤ 1ኛ ጸሎት

          2ኛ የእግዚአብሔር ቃል

          3ኛ የአማኞች ኅብረት ናቸው፡፡

1. ጸሎት

ጸሎት ለአንድ ክርስቲያን ዕድገት ከሚያስፈልጉት ነገሮች ዋነኛው ነው፡፡ ለአንድ ተክል ዕድገት አየር እንደሚያስፈልገው ሁሉ የአንድ ክርስቲያን አየር ወይም ትንፋሽ ጸሎት ነው፡፡ አንድ ሰው ሳይተነፍስ ብዙ መቆየት አይችልም፡፡ አንድ ክርስቲያንም መጸለይ ካቆመ መንፈሳዊ ትንፋሽ እያጠረው ይሄዳል፤ ይዝላል፤ ይጠወልጋል በኋላም ከጌታ እየራቀ ወደ ድሮ ሕይወቱ ይመለሳል ስንተነፍስ የተቃጠለውን አየር ወደ ውጭ፤ አዲስን አየር ደግሞ ወደ ውስጥ እንደምናስገባ፤ ስንጸልይም ኃጢአታችንንና ድካማችንን በንሥሓ ጸሎት ወደ ውጭ አስወጥተን አዲስ ጸጋንና ምሕረትን ደግሞ ወደ ውስጥ የምንቀበልበት መንገድ ነው፡፡

 

ሀ. ጸሎት ምንድን ነው@

ጸሎት፤ አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በመንፈሱ ግንኙነት ሲያደርግ ማለት ነው፡፡ የልቡን ሐዘን ሆነ ደስታ፤ ምሥጋናም ሆነ የሆድ ብሶት፤ ልመናም ሆነ አምልኮ ለእግዚአብሔር ሲያስታውቅና እግዚአብሔር ደግሞ ለልቡ የሚናገረውን ሲያዳምጥ ነው፡፡ ትክክለኛ ጸሎት ለእግዚአብሔር መናገር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ለልባችን የሚናገረንንም መስማት ያጠቃልላል፡፡ በጽሞና ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል ስናነብ ይናገረናል ወይንም በቀጥታ ለልባችን ይናገረናል፡፡ (አሞ. 4$13)

በአጠቃላይ ጸሎት ማለት ከሰማያዊው አባታችን ጋር በየጊዜው መነጋገር ማለት ነው፡፡ ከአባቱ ጋር የማይነጋገር ልጅ ችግር አለበት፡፡ ከእግዚአብሔርም ጋር በየጊዜው የማንነጋገር ከሆነ አንድ ማስተካከል ያለብን ነገር አለ ማለት ነው፡፡

ለ. የተለያዩ የጸሎት ዓይነቶች አሉ

1. የንሥሐ ጸሎት

ይህ የጸሎት ዓይነት ከሌሎቹ የጸሎት ዓይነቶች ሁሉ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ነው ምክንያቱም ኃጢአት በእኛና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ግንኙነት ስለሚያቋርጥ ቶሎ ብለን የተቋረጠውን ግንኙነት በንሥሐ ማስተካከል አለብን፡፡

‹‹እነሆ የእግዚአብሔር እጅ ከማዳን አላጠረችም፤ ጆሮውም ከመስማት አልደነቆረችም፤ ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች፤ እንዳይሰማም ኃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል፡፡››  ኢሳ. 59$1-2

በተለይ ኅሊናችን በግልጽ የሚወቅሰን ኃጢአት ካለ ቶሎ በንሥሐ ከእግዚአብሔር ይቅርታን መቀበል አለብን፡፡

‹‹በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው፡፡›› 1ዮሐ. 1$9

      ልጆቼ ሆይ፤ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ፡፡ ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን፤ እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ 1ዮሐ. 1$7፤ 2$1

የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል፡፡

ኅሊናችንን የሚወቅሰን ነገር ከሌለ ግን ለጸሎት በተንበረከክን ቊጥር የንሥሐ ጸሎት መጸለይ የለብንም፡፡ ‹‹ወዳጆች ሆይ ልባችንስ ባይፈርድብን በእግዚአብሔር ዘንድ ድፍረት አለን፡፡›› 1ዮሐ. 3$21

አንዳንድ ጊዜ ግን ከእኛ የተሰወረ ኃጢአት ሊኖር ስለሚችል እንደ ዳዊት

‹‹ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ›› ማለት ይኖርብናል፡፡ መዝ. 19$12

2. የልመና ጸሎት

ይህ ጸሎት፤ የሚያስፈልገንን ነገሮች ከእግዚአብሔር የምንለምንበት ጸሎት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ‹‹ለምኑ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል፡፡ የሚለምን ሁሉ ይቀበላል›› ማቴ. 7$7-8 ባለው መሠረት የሚያስፈልገንን ነገር ለመለመን የልጅነት መብት ተሰጥቶናል፡፡

ይህ ጸሎት የሚያስጨንቀንን ነገር ሁሉ በእርሱ ላይ የምንጥልበት ጸሎት ነው፡፡

‹‹በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምሥጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ፡፡›› ፊልጵ. 4$6

‹‹እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት፡፡›› 1ጴጥ. 5$7

ለዚህ ለልምና ጸሎት ከእግዚአብሔር ሦስት ዓይነት መልሶችን ማግኘት እንችላለን፡፡

ሀ. እሺ- የለመንነው ነገር ለሕይወታችን አስፈላጊና እግዚአብሔርን የሚያስከብር ከሆነ እሺ ብሎ ልመናችንን ይሰጠናል፡፡

እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር አያሳጣቸውም፡፡ መዝ. 84$11

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝም የለም፡፡ መዝ. 23$1

ለ. ቆይ የለመንነው ነገር ለሕይወታችን የሚያስፈልግና ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን ቢሆንም፤ የእግዚአብሔር ጊዜ ከእኛ ጊዜ ስለሚለይ ቆይ የሚለን ጊዜ አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከለመንነው ነገር ይልቅ ይበልጥ የሚያስፈልገን ትዕግሥት ስለሆነ መልሱ ይዘገያል፡፡ አንዳንድ ጊዜ እምነታችን እንዲያድግ ስለሚፈልግ ባሰብነው ጊዜ አይሰጠንም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ያንን የለመንነውን ነገር ለመቀበል ገና ስለሆንን እኛ እስከምሠራና ("ን" ጠበቅ ብሎ ይብ) እስከምንዘጋጅ መልሱ ይቆያል፡፡

በአጠቃላይ ጠቢቡ ሰሎሞን፤ ለሁሉ ‹‹ዘመን (ጊዜ) አለው፤ ከሰማይ በታችም ለሆነ ነገር ሁሉ ጊዜ አለው፡፡›› (መክ. 3$1) ብሎ እንደተናገረው የልመናችን መልስ የተመደበለትን የእግዚአብሔርን ጊዜ መጠበቅ ይኖርበታል፡፡

ሐ. እምቢ፤ ልጆ የሚለምኑትን ልመና ሁሉ እሺ የሚል ምድራዊ አባት አለ ማለት ያስቸግራል፤ ካለ ትንሽ የአእምሮ ቀውስ አለበት ማለት ነው፡፡ የሰማዩ አባታችን፤ እግዚአብሔርም ሳናውቅ ባለማስተዋል የምንለምነውን ልመና እምቢ ይለናል፡፡ ማታ. 20$20-22

 

የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለው ሰዎች ከእግዚአብሔር የማይቀበሉበት ምክንያቶች ሦስት ናቸው፡፡

1. ስለማንለምን፤ ‹‹አትለምኑምና አታገኙም›› ያዕ. 4$2

2. የምንለምነው ነገር እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካልሆነ ያዕ. 4$3፤ 1ዮሐ. 5$14-15

3. በልባችን ኃጢአት ሲኖር፤ ‹‹በልቤስ በደልን አይቼ ብሆን ጌታ አይሰማኝም ነበር፡፡›› መዝ. 65(66)፡18

 

3. የምልጃ ጸሎት

ለራሳችን ሳይሆን ለሌሎች መንፈሳዊም ሆነ ሥጋዊ ችግር የምንጸልየው ጸሎት ነው፡፡

ሀ. እኛ ራሳችን ለእከሌ ልጸልይ ብለን የምንፈጸልየው ጸሎት፡፡

‹‹በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምሥጋና ጋር ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ፡፡›› ፊል. 4$6

በአንድ ሰው ሕይወት ድካም ስናይ ከድካሙ ነጻ እንዲሆን እንድንማልድለት እንጂ እንድንፈርድ አልተፈቀደልንም፡፡ ሮሜ 14$1፤ 1ዮሐ. 5$16)

ለ. መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ ሆኖ የሚማልደው ጸሎት፡፡ ይሄ ጸሎት መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሆኖ ነገር ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲከናወን የሚያቀርበው ጸሎት ነው፡፡

‹‹እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንዲገባን አናውቅምና፣ ነገር ግን መንፈስ ራሱ (እግዚአብሔር) የመንፈስ ሐሳብ ምን እንደሆነ ያውቃል እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ ቅዱሳን ይማልዳልና፡፡›› ሮሜ 8$26-27)

ሐ. የምልጃን ጸሎት ማቅረብ የሚችል በሕይወት ያለ ሰው እንጂ የሞቱ ጻድቃንና ሰማዕታት ወይም መላእክት አይደሉም፡፡ መክ. 9$4-6፤ ራዕ. 22$8-9

 

4. የምሥጋና ጸሎት

ይህ ጸሎት ከሌሎቹ ይልቅ ይበልጥ መለማመድ ያለብን የጸሎት ዓይነት ነው፤ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር ፍጹም ኅብረት የሚኖረን እግዚአብሔርን በምሥጋና በምናመልክበት ጊዜ ነው፡፡

ሁለት ዓይነት የምሥጋና ጸሎት አለ፤

ሀ. እግዚአብሔር ስላደረገልን ነገሮች እግዚአብሔርን ማመስገን፡፡ መዝ. 103$1-5፤

ለ. ስለ እግዚአብሔር ማንነት እግዚአብሔርን ማመስገን፡፡

            መዝ. 117(118)፡1፤ ኢዮ. 1$21፤ 42$2

5. የሥልጣን ጸሎት

ይህ ጸሎት እግዚአብሔር የሰጠንን የልጅነት ሥልጣን ተጠቅመን ሰይጣንን የምንቃወምበት ጸሎት ነው፡፡ ሰይጣንንም የምንቃወመው

ሀ. በኢየሱስ ስም

ለ. በኢየሱስ ደም

ሐ. በእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡

‹‹እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ ዲያብሎስን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል፡፡›› ያዕ. 4$7-8

 

2. የእግዚአብሔር ቃል

አንድ ተክል ከአየር ሌላ ውሃና ማዕድን (ምግብ) እንደሚያስፈልገው ሁሉ፣ አንድ ክርስቲያንም ለማደግ የእግዚአብሔርን ቃል በየዕለቱ መመገብ አለበት፡፡

 ‹‹እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኮልንም ሁሉ ግብዝነትንም ሁሉ ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፤ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደሆነ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደተወለዱ ሕፃናት ተንኮል የሌለበትን የቃሉን ወተት ተመኙ፡፡›› 1ጴጥ. 2$1-3

የእግዚአብሔር ቃል በሕይወታችን ሊኖረው የሚገባው ስፍራ

ሀ. ብርሃናችን ነው፡፡ ‹‹ሕግህ ለእግሬ መብራት፣ ለመንገዴም ብርሃን ነው፡፡›› (መዝ. 118$105)

ለ. መንገዳችንን ያነጻል፡፡ ‹‹ጐልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል@ ቃልህን በመጠበቅ ነው፡፡›› መዝ. 118$9

ሐ. ሕይወታችንን ያንጻል፡፡ ‹‹አሁንም ለእግዚአብሔርና፣ ያንጻችሁ ዘንድ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ይሰጣችሁ ዘንድ ለሚችል ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ፡፡›› ሐዋ. 20$32

መ. ከእግዚአብሔር የተሰጠንን መንፈሳዊ ርስት ያሳየናል፡፡ ሐዋ. 20$32 ይህ ርስት የእግዚአብሔር የተስፋ ቃሎች ናቸው፡፡

ሠ. መንፈሳዊ ሰይፋችን ነው፡፡ ‹‹የመንፈስን ሰይፍ ያዙ፤ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡›› ኤፌ. 6$17

ረ. መንፈሳዊ ምግባችን ነው፡፡ ‹‹... አሁን እንደተወለዱ ሕፃናት የቃሉን ወተት ተመኙ፡፡›› 1ጴጥ. 2$1-3

ሰ. እውነትን የምናውቅበት መንገድ ነው፡፡ ‹‹የእውነትን ቃል እርግጥነት አስታውቅህ ዘንድ፣ ለሚጠይቅህም የእውነትን ቃል መመለስ ይቻልህ ዘንድ፣ በምክርና በእውቀት የከበረን ነገር አልጻፍኩልህምን@›› ምሳሌ 22$20-21

እውነት ደግሞ ነፃ ያወጣናል ዮሐ. 8$32፤ ያዕ. 1$25

ሸ. የማስተዋልና የጥበብ ምንጭ ነው፡፡ ‹‹ትእዛዝህ (ቃልህ) ከጠላቶ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ፡፡ ... ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልኩኝ፡፡ ትእዛዝህን (ቃልህን) ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ (አስተዋልኩኝ)፡፡›› መዝ. 118$98-100፤ ምሳሌ 1$1-7

ቀ. ከስህተት የምንጠበቅበት መመሪያችን ነው፡፡

‹‹መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ፡፡›› ማቴ. 22$29

በ. ሕይወታችንን የሚያጠራ እሳት ነው፡፡

‹‹በውኑ ቃሌ እንደ እሳት፣ ድንጋዩንም እንደሚያደቅቅ መዶሻ አይደለችምን›› ኤር. 23$29

ተ. የደነደነውን ልባችንን የሚሰብር መዶሻ ነው፡፡ ኤር. 23$29፡፡

ቸ. ልብንና ኩላሊትን (የሰውን የውስጥ አሳብ) የሚመረምር መንፈሳዊ ራጂ (X-ray) ነው፡፡

‹‹የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና የሚሠራም፣ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፤ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፤ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፡፡›› ዕብ. 4$12

የእግዚአብሔር ቃል ከላይ የተጠቀሱትን ነገሮች የሚሆንልን ስናነበውና ስንሰማው ብቻ ሳይሆን ሰምተን ሥራ ላይ ስናውለው ነው፡፡

‹‹ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ፡፡›› ያዕ. 1$22-25

 

3. ከአማኞች ጋር ኅብረት ማድረግ፣

አንድ ተክል ከአየርና ከምግብ ሌላ የፀሐይ ብርሃን እንደሚያስፈልገው ሁሉ፤ አንድ አማኝም እውነተኛ ክርስትያኖች ወዳሉበትና የእግዚአብሔር መንፈስ ወደሚሠራበት ስፍራ ከሌሎች አማኞች ጋር ኅብረት ለማድረግ መንገዱን ወደዚያ መቅናት አለበት፡፡ አንዲት ፍም ለብቻዋ ብትሆን በአካባቢው ነፋስ ቶሎ እንደምትከስም እኛም እርስ በርስ ካልተሟሟቅን እንቀዘቅዛለን፡፡

ከሎሎች አማኞች ጋር ኅብረት ማድረግ ያለብን ለምንድነው@

1.     እግዚአብሔር ልዩ የሆነ በረከትን በዚያ ስፍራ ስለሚያፈስ

   ‹‹ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው፣ እነሆም ያማረ ነው፤ ... በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዞአልና፡፡›› መዝ. 133

2.     ጌታ ኢየሱስ በመካከላችን ስለሚገኝ (ማቴ. 18$20)

   እንደውም መሰብሰብ ያለብን ከእርሱ ለመስማትና ለመቀበል እንጂ ሰውን ለማየት መሆን የለበትም፡፡

3.     ፍቅርን ለመስጠትና ለመቀበል፤ ዮሐ. 13$34-35፤ ዕብ. 10$24-25

4.     ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ ኤፌ. 2$